Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ዓለም አቀፉ ግብረ ሠናይ ድርጅት በኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ለሚገኙ ሴት ተፈናቃዮች የሚውል የ1 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አገኘ

አዲስ አበባ ፣ ጥር 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “አክሲየን” የተሰኘ ዓለም አቀፍ ግብረ-ሠናይ ድርጅት በኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ለሚገኙ ሴት ሥደተኞች ድጋፍ የሚያውለው 1 ሚሊየን ዶላር ከኮናርድ ሂልተን ፋውንዴሽን ማግኘቱን አስታወቀ፡፡

ግብረ-ሠናይ ድርጅቱ ÷ ሥደተኞቹ በሚገኙበት ሀገር ከሚሠሩ የፋይናንስ ፣ የንግድ እና የማኅበረሰብ ተቋማት ጋር በመተባበር ሥራ መጀመር የሚያስችላቸውን መነሻ ገንዘብ እና ሥልጠና እንደሚያመቻች ዛሬ በገፁ ባወጣው መረጃ አመላክቷል፡፡

በኢትዮጵያ እና በኡጋንዳ ገጠራማ የሀገራቱ ክፍሎች ከመሠረታዊ አገልግሎቶች የተገለሉ ከ 2 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሥደተኞች መሥፈራቸውንም ነው የጠቆመው፡፡

የአሲየን ግብረ-ሠናይ ድርጅት ፕሬዚዳንት እና ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ሚካዔል ሽላይን ÷ ሴት ሥደተኞቹ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ ከሂልተን ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር እንሠራለን ብለዋል፡፡

በሚኖሩበት ማኅበረ-ሰብ ውስጥ በአነስተኛ ንግዶች ላይ ተሠማርተው በኢኮኖሚ ጠንካራ የሚሆኑበት መንገድ እንዲፈጠር እና ከራሳቸው አልፈው አካባቢያቸውን በኢኮኖሚ እንዲገነቡ ብድር እንደሚያቀርቡም ተመልክቷል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version