Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዜጎች ፍትሃዊ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት አለባቸው – አቶ አገኘሁ ተሻገር

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት በመፍጠር የዜጎችን ፍትሃዊ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች መመለስ አለብን ሲሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ውይይት እየተካሄደ ነው።

የውይይት መድረኩ በቀጣይ ሕገ-መንግስታዊነትን ፣ የዴሞክራሲ ሥርዓትን እና ዘላቂ ሠላምን በሀገሪቱ ለማስፈን ያለመ ነው ተብሏል።

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ከ4 ዓመት በፊት ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ማድረጉን እና የነበረበትን ክፍተት መሙላቱን አስታውቋል፡፡

አቶ አገኘሁ ተሻገር ÷ ምክር ቤቱ ከሀገራዊ እና መንግስታዊ ተልዕኮ ባለፈ ከሲቪል ማኅበረሰቡ ጋር በትብብር እና በቅንጅት ይሠራል ብለዋል።

በምንይችል አዘዘው እና ሲሳይ ዱላ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version