Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ደመቀ መኮንን በደቡብ ሱዳን የኢጋድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በደቡብ ሱዳን የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኢስማኤል ዋይስ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም ኢትዮጵያ እና ኢጋድ በቀጣናው ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ተባብረው ሊሠሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

Exit mobile version