Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያና ቻይና በግብርናው ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ለማደስ ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያና ቻይና በግብርናው ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ለማደስ ተሥማሙ፡፡

አምባሳደር ተፈራ ደርበው በቻይና የግብርና ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ አጋርነት ክፍል ኃላፊ ከሆኑት ኒ ሆንግሺንግ እንዲሁም በምዕራብ እስያ እና አፍሪካ ጉዳዮች የዓለም አቀፍ ትብብር ሊዩ ጂያንግ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸው ወቅት ሀገራቱ ቀደም ሲል በግብርናው ዘርፍ የደረሱትን የመግባቢያ ሰነድ አንስተው መክረዋል።

በዚህ ወቅትም ስምምነቱን ወደ ትግበራ መቀየር በሚቻልባቸው አስቻይ ሁኔታዎች ላይ መወያየታቸውም ነው የተመለከተው፡፡

ሁለቱም ወገኖች በመደበኛነት ለመገናኘት እና በግብርናው ዘርፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ለመቀጠል ተሥማምተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version