Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ ዘንድሮ ከመከላከያ ጡረታ መውጣቴ ቁርጥ ነው አሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ ጀነራል ሙሁዚ ካይኔሩጋባ ዘንድሮ ከሀገሪቷ መከላከያ በጡረታ እንደሚወጡ በትዊተር ገፃቸው አስታወቁ፡፡

የጦር ጄኔራሉ በትዊተር ገጻቸው ይህን ያሉት በዩጋንዳ መከላከያ ሠራዊት ውስጥ ለ30 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ ካገለገሉ በኋላ መሆኑን ቢቢሲ አስታውሶ ዘግቧል፡፡

ያሁኑ ጀኔራል ካይኔሩጋባ አምና መጋቢት ወር ላይ የምድር ጦር አዛዥ በነበሩበት ወቅትም ተመሳሳይ የ“ጡረታ መውጣቴ ነው” መልዕክት በትዊተር ገጻቸው አስነብበው ነበር ተብሏል፡፡

ነገር ግን በወቅቱ መከላከያ ኃይሉ የፕሬዚዳንቱን ልጅ የጡረታ ጥያቄ ውድቅ እንዳደረገባቸው እና ሥራቸውን እንደቀጠሉ ተነግሯል፡፡

ጄኔራሉ በፈረንጆቹ 2026 ላይ ለፕሬዚዳንትነት እወዳደራለሁ ብለው በትዊተር ገጻቸው ካሰፈሩ በኋላ ያስነበቡትን ሐሳባቸውን መልሰው መሰረዛቸውንም ዘገባው አስነብቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version