Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በመኖሪያ ቤታቸው የአፍጥር ዝግጅት አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በመኖሪያ ቤታቸው የአፍጥር ዝግጅት አካሂደዋል፡፡

በሥነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼክ ሃጂ ኢብራሂም፣ የምክር ቤቱ አባላትና የእምነቱ አባቶች ተገኝተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ባለፈው ዓመትም በመኖሪያ ቤታቸው የአፍጥር ዝግጅት ማካሄዳቸው ይታወሳል፡፡

Exit mobile version