Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በቱርክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት ለደረሰባቸው ቱርካውያን ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 3 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቱርክ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ክፍሎች በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ቱርካውያን አስቸኳይ የቁሳቁስ፣ የገንዘብ፣ እና የጉልበት ድጋፍ ማድረጋቸው ተገለጸ፡፡

ድጋፉን በሀገሪቷ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመተባበር አድርገዋል ነው የተባለው፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ከቱርክ ጋር ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳለው ይታወቃል፡፡

እንደሚታወሰው አደጋው በደረሰበት ወቅትም ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከፌዴራል ፖሊስ እና ጤና ሚኒስቴር የተውጣጣና 27 የፍለጋ እና ሕይወት አድን ባለሙያዎች ቡድን ከዕርዳታ ቁሳቁስ ጋር ወደ ሥፍራው መሄዱ አይዘነጋም፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version