Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ ሀገር-በቀል ኢኮኖሚ ላይ በትኩረት እንደምትሠራ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ ሀገር-በቀል ኢኮኖሚ ላይ በትኩረት እንደምትሠራ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ አስታወቁ።

ሚኒስትሩ “ከዕዳ መውጣት ፣ ዕድገት ማስመዝገብ” በሚል መሪ ቃል አሜሪካ በተዘጋጀው በዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ መድረክ የፓናል ውይይት ላይ ተሳትፈዋል።

ዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም እንዲሁም የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ተዋንያን እና ሌሎች የገንዘብ ተቋማት ኢትዮጵያ የምንዛሬ አቅርቦት ዕጥረቷን ለመፍታት የምታደርገውን ጥረት እንዲደግፉ ጠይቀዋል፡፡

በጉባዔው ከዓለም ባንክ በተጨማሪ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም እንደተካፈለም ተጠቁሟል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version