Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

መንግስት በሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኤፌዴሪ መንግሥት በሱዳን ባለው ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት በሀገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዋናው መስሪያ ቤት እና ካርቱም በሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ አማካኝነት የኢትዮጵያውያንን ደኅንነት ለመጠበቅ እየሠራ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች እና አጎራባች ክልሎች አባል የሆኑበት ግብረ ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ መቋቋሙም ነው የተመለከተው፡፡

አስፈላጊ መረጃዎችን በቀጣይ እንደሚያሳውቅም ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የገለጸው፡፡

Exit mobile version