Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል 30 ኪሎ ግራም የሚመዝን እንቁልጢ በቀዶ ጥገና ሕክምና ተወገደ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል 30 ኪሎ ግራም የሚመዝን እንቁልጢ (Ovarian Tumer) በቀዶ ጥገና ሕክምና መወገዱ ተገለጸ፡፡

የሆስፒታሉ የማሕጸንና ጽንስ እስፔሻሊስት ዶክተር ግላንዴ ግሎ፥ የቀዶ ጥገና ሕክምናው 1 ሠዓት ከ30 ደቂቃ የፈጀ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን ላይ ታካሚዋም በሙሉ ጤንነት ላይ እንደምትገኝ ተነግሯል፡፡

ዶክተር ግላንዴ የማሕፀን ዕጢ ብዙ ጊዜ በመውለድ ዕድሜ ክልል ውስጥ በሚገኙ ሴቶች የተለመደ ቢሆንም አልፎ አልፎ ግን ህፃናት እንዲሁም የወር አበባ ማየት ያቆሙ ሴቶች ጭምር ላይ ሊከሰት እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን እስከ አሁን ከ15 ኪሎግራም በላይ የሚመዝን ዕጢ እምብዛም ያልተለመደ ነው ማለታቸውን ከጎፋ ዞን ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version