Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ ከላቲን አሜሪካና መካከለኛው እስያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሥፋት እየሠራች ነው – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ ከላቲን አሜሪካና መካከለኛ እስያ ጋር ያላትን የግንኙነት አድማስ ለማስፋት ውጤታማ ሥራዎች እየሠራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

የሚኒስቴሩ ቃል-አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በሰጡት መግለጫ ÷ ኢትዮጵያ ከኮሎምቢያና ፓኪስታን ጋር ያላትን የፖለቲካ ግንኙነት በዘርፈ ብዙ የትብብር መስኮችን ለማስቀጠል ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ናቸው ብለዋል፡፡

የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍራንሲያ ኤሌና ማርኬዝ በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት እያደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ምክትል ምክትል ፕሬዚዳንቷ በቆይታቸው ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት እንዳደረጉ አምባሳደሩ ገልፀዋል።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ የተመራው ልዑክም ባሳለፍነው ሳምንት በፓኪስታን ቆይታ ማድረጉን አንስተዋል፡፡

በሀገራቱ መካከል የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ ከፋች የሆኑ ዲኘሎማሲያዊ ተግባራት እንደተፈፀሙም ነው ያስታወቁት።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version