Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጃፓን “ኔቶ”ን የመቀላቀል ዕቅድ የላትም – ፉሚዮ ኪሺዳ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጃፓን የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል-ኪዳን ድርጅት “ኔቶ”ን የመቀላቀል ዕቅድ እንደሌላት የሀገሪቷ ጠቅላይ ሚኒስትር ፉሚዮ ኪሺዳ አስታወቁ፡፡

ፉሚዮ ጃፓን በማናቸውም መንገዶች አሜሪካ መራሹን የጦር ቃል-ኪዳን ድርጅት አትቀላቀልም ሲሉ አቋማቸውን ያስታወቁት በዛሬው ዕለት በተካሄደው የሀገሪቷ ፓርላማ ስብሰባ ላይ ነው፡፡

አሁን የተሰማው የጠቅላይ ሚኒስትሩ አቋም በአሜሪካ የጃፓን አምባሳደር የሆኑት ኮጂ ቶሚታ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ከሰጡት መግለጫ ጋር የማይጣጣም መሆኑን አር ቲ ሬውተርስን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡

በወቅቱ አምባሳደሩ በእስያ የመጀመሪያ ይሆናል ያሉትን የ”ኔቶ” ጽኅፈት ቤት በቶኪዮ ለመክፈት ጃፓን እየሰራች መሆኑን ጠቁመው ነበር፡፡

የጦር ቃል ኪዳን ድርጅቱም በሕንድ-ፓሲፊክ ቀጣና የመወከል ፍላጎት እንዳለው አልሸሸገም፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ፉሚዮ ÷ የጦር ቃል-ኪዳን ድርጅቱ ሥራዎቹን ለማሳለጥ ያመቸው ዘንድ በጃፓኗ ቶኪዮ ቢሮ ለመክፈት መጠየቁን አረጋግጠዋል፡፡

ሀገራቸው ግን ይሆናልም ፣ አይሆንምም የሚል ምላሽ አልሰጠችም ነው ያሉት፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version