Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የአንድነት ፓርክ የዕጽዋት ማዕከልን መርቀው ከፈቱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአንድነት ፓርክ የዕጽዋት ማዕከልን፣ የአንድነት ቤተ መዛግብትን እና የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የሕክምና ማዕከልን መርቀው ከፈቱ።

የማዕከላቱን መመረቅ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በኩል የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ የዕጽዋት ማዕከሉ ጥቅም ላይ ውሎ በማያውቅ ቦታ ላይ የተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ለአንድነት ቤተ መዛግብት እና ለሕክምና ማዕከሉ ደግሞ ሰፋፊ የማዘመን ሥራዎችን በማከናወን ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ መደረጉን ነው ያመለከቱት።

አያይዘውም ቦታን በበቂ እና ውጤታማ በሆነ መንገድ መጠቀም እሴት ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

Exit mobile version