አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የምትካፈልበት የ5 ሺህ ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ውድድር ምሽት 2 ሰዓት ላይ ይካሄዳል፡፡
በሀንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ የሚገኘው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ስድስተኛው ቀኑን ይዟል፡፡
በዛሬው እለትም የ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ምሽት 2 ሰዓት ላይ የሚካሄድ ሲሆን÷ ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ሀጐስ ገ/ሕይወት እና በሪሁ አረጋዊ ኢትዮጵያን ወክለው እንደሚሳተፉ የአትሌቲክስ ፌደሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡