Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ዓመታዊውን የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ በመጪው ዓርብ በይፋ ይጀምራል- ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓመታዊውን የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ በመጪው ዓርብ በይፋ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስታወቁ።

ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጋር እየተፋለምን ቢሆንም፤ 5 ቢሊየን ችግኞችን የመትከል ዕቅዳችንን እናሳካዋለን ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

እያንዳንዱ ቤተሰብ አካላዊ ርቀትን እንደ ጠበቀ ዐሻራውን ማሳረፍ የሚችልበትን መንገድ እንደሚመቻች ተጠቁሟል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፈው ዓመት እያንዳንዳችን ሀገራዊ ጥሪውን ተቀብለን ያቀድነውን አሳክተናልም ነው ያሉት በፌስቡክ ገፃቸው።

Exit mobile version