Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የድርሻ ገበያ እና ልውውጥ መጀመር ኢትዮጵያ የእድገት ትልሟ እውን እንዲሆን አዳዲስ ካፒታል በመሳብ ጨዋታ ቀያሪ ይሆናል- ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የድርሻ ገበያ እና ልውውጥ (ስቶክ ማርኬት ኤንድ ኤክስቼንጅ) መጀመር ኢትዮጵያ የእድገት ትልሟ እውን እንዲሆን አዳዲስ ካፒታል በመሳብ ጨዋታ ቀያሪ ይሆናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ቦርድ÷ ኢትዮ ቴሌኮም ሕዝባዊ ለመሆን ያለውን ዝግጁነት እና የካፒታል ማርኬት ባለስልጣን በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያን ወደሥራ በማስገባት ላይ የደረሰበትን ደረጃ ገምግሟል፡፡

ይህን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው÷ በኢትዮጵያ የድርሻ ገበያ እና ልውውጥ (ስቶክ ማርኬት ኤንድ ኤክስቼንጅ) መጀመር ኢትዮጵያ የእድገት ትልሟ እውን እንዲሆን አዳዲስ ካፒታል በመሳብ ጨዋታ ቀያሪ ይሆናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ይህም ለሀገራችን አጓጊ አዲስ ምዕራፍ ነው ብለዋል፡፡

Exit mobile version