Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ማውን ከተማ በረራ እንደሚጀምር አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቦትስዋና ማውን ከተማ በረራ እንደሚጀምር አስታወቀ።

አየር መንገዱ በረራውን ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ.ም የሚጀመር መሆኑን የገለፀ ሲሆን በሳምንት ሶስት ቀን ወደ ከተማዋ በረራ እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡

አየር መንገዱ በረራ ሲጀምር ማውን ከተማ በቦትሰዋና ሁለተኛዋ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መዳረሻ እንደምትሆን ተመላክቷል፡፡

Exit mobile version