Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቀብሪደሃር በሣምንት 2 ቀን ለመብረር ዝግጅቱን አጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሶማሌ ክልል ቀብሪደሃር ከተማ በሣምንት ሁለት ቀን የበረራ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

የሀገር ውስጥ የበረራ አድማሱን እያስፋፋ መሆኑን ያስታወቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ÷ በሶማሌ ክልል ብቻ ቀብሪደሃር ከጂግጂጋ እና ጎዴ ቀጥሎ ሦስትኛ መዳረሻው መሆኑን ገልጿል፡፡

Exit mobile version