Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት በመዲናዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ጎበኙ፡፡

በጉብኝታቸውም÷በከተማዋ አምስቱም የኮሪደር ልማት መስመሮች እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች የደረሱበትን ደረጃ ተዘዋውረው መመልከታቸው ተገልጿል፡፡

ከኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በልማቱ ምክንያት የተነሱ ነዋሪዎች ያረፉባቸውን መኖሪያ ቤቶች እየጎበኙ መሆኑን የም/ቤቱ መረጃ አመልክቷል፡፡

Exit mobile version