የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት በመዲናዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ጎበኙ፡፡
በጉብኝታቸውም÷በከተማዋ አምስቱም የኮሪደር ልማት መስመሮች እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች የደረሱበትን ደረጃ ተዘዋውረው መመልከታቸው ተገልጿል፡፡
ከኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በልማቱ ምክንያት የተነሱ ነዋሪዎች ያረፉባቸውን መኖሪያ ቤቶች እየጎበኙ መሆኑን የም/ቤቱ መረጃ አመልክቷል፡፡