Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ ባሕርዳር ገባ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ ባሕርዳር ከተማ ገብቷል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ የጣና ሐይቅ ፈርጧ፣ የበርካታ ደሴቶች መናኸሪያ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ መገኛ እና የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ በሆነችው ውቢቷ ባሕርዳር ገብተናል ብለዋል።

ልዑኩ ባሕር ዳር ሲደርስም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እና ካቢኔያቸው አቀባበል አድርገውለታል።

Exit mobile version