Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠ/ሚ ዐቢይ የሁለት ቀን የኤርትራ ጉብኝታቸውን  አጠናቀው አዲስ አበባ ተመለሱ

አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 12 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ እና ልኡካቸው የሁለት ቀን ይፋዊ የኤርትራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ሐምሌ 12 ቀን 2012 ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

ጉብኝቱ የኢትዮጵያንና የኤርትራ የሰላም ስምምነት አዲስ ምዕራፍ ከተደረሰ እና የሀገራቱ መልካም ጉርብትናና የዲፕሎማሲያዊ የግንኙነት ከተበሰረ ሁለት ዓመት በኋላ የተካሄደ ነው፡፡

ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ እንዲሁም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችንም ጎብኝተዋል፡፡

 

Exit mobile version