Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ባጋጠመው ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ግምገማ እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 2 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ባጋጠመው ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ግምገማ እያካሄደ ነው፡፡

ግምገማው በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

በግምገማው ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

Exit mobile version