Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ፣ግብጽና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት እያካሄዱ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ፣ግብጽና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ዛሬ በሱዳን ካርቱም የሶስትዮሽ ውይይት እያካሄዱ ነው፡፡

የሶስቱ ሀገራት ውሃ ሚኒስትሮች በካርቱም በግድቡ ውሃ አሞላል እና አለቃቀቅ ዙሪያ ትኩረት በማድረግ እንደሚወያዩ ተነግሯል፡፡

ይህ ውይይቱ በአለም ባንክ እና አሜሪካ ታዛቢነት ከሚካሄዱት አራት ስብሰባዎች ሶስተኛው መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ውይይት ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ፣ ካይሮ እንዲሁም በዋሽንግተን መካሄዱ የሚታወስ ነው፡፡

Exit mobile version