Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳዳር ይበልጣል አእምሮ ከካርቱም ስቴት ገዥ አይማን ካሊድ መሀመድ ካልድ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በካርቱም የኢፌዴሪ ልዩ መልዕከተኛና ባለመሉ ስልጣን አምባሳዳር ይበልጣል አእምሮ ከካርቱም ስቴት ገዥ አይማን ካሊድ መሀመድ ካልድ ጋር ተወያዩ፡፡

አምባሳደሩ ስለ ወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይና ህግ ማስከበር ስራ ላይ ገለፃ አድርገዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በሱዳን ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት ክለብ የሚያገለግል ተጨማሪ ቦታ እንዲሰጥ ለአስተዳዳሪው ጥያቄ ማቅረባቸውን በሱዳን የኢትዮጵያ ኢምባሲ አሳውቋል፡፡

Exit mobile version