Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አንቶኒ ብሊንኬን በጆ ባይደን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው መታጨታቸውን ይፋ አደረጉ

Deputy Secretary of State Antony Blinken testifies on Capitol Hill in Washington, Tuesday, Jan. 27, 2015, before the Senate Banking Committee hearing on Iran sanctions. A group of Senate Democrats told the White House on Tuesday that they won't support passage of an Iran sanctions bill until at least the end of March. (AP Photo/Susan Walsh)

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 15 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ. ሲ) አንቶኒ ብሊንኬን በተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ቀጣዩ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው መታጨታቸውን ይፋ አደረጉ።
እጩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ባለፉት ቀናት ከስራ ባልደረቦች እና ጓደኞች የደረሱኝ መልዕክቶች ኩራትን የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል በትዊተር ገፃቸው ላይ።
በጆ ባይደን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆኘ መታጨቴን ስገልፅ ኩራት ይሰማኛል ነው ያሉት አንቶኒ ብሊንኬን።
ይህ ተልዕኮ በሙሉ ልቤ የሚፈፅመው መሆኑን ላረጋገጥላችሁ አፈልጋለሁም ብለዋል።
አንቶኒ ብሊንኬን በባራክ ሁሴን ኦባማ ዘመን አስተዳደር ከፈረንጆቹ 2015 እስከ 2017 የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
እንዲሁም ከ2013 እስከ 2015 ደግሞ ምክትል የብሄራዊ ደህነነት አማካሪ በመሆን መስራታቸውም ተነግሯል።
በተመሳሳይ ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአሜሪካ አምባሳደር ሆነው መታጨታቸውም ይፋ ሆኗል።
እጩ አምባሳደሯ በባራክ ሁሴን ኦባማ ዘመን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር ነበሩ።
Exit mobile version