አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አደም መሃመድ ከኳታር አቻቸው ሌተናል ጀኔራል ጋህነም ቢን ሻሂን አል ጋህኒም ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም ሀገራቱ ያላቸውን ወታደራዊ ግንኙነት የጋራ ጥቅምን ባስከበረ መልኩ ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ መክረዋል።
በኳታር ዶሃ በተካሄደው በዚህ ውይይት ከሁለቱ ሀገራት የተውጣጡ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች ተሳትፈዋል።