Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከኔዘርላንድስ ጠ/ሚ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩት ጋር ተወያዩ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና ማርክ ሩት በሀገራቱ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ነው የተወያዩት፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በውይይቱ ወቅት በቀጠናው ሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ መምክራቸውን አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከኔዘርላንድስ ጋር በዲፕሎማሲ፣ በንግድ እና በኢንቨስትመንት በኩል ያላት የቆየ ግንኙነት ለቀጣይ ግንኙነት መሰረት ነው ብለዋል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፦ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ዩቲዩብ ቻናል፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version