Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ የነበረ 51 ሺህ 700 የአሜሪካ ዶላር በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ የነበረ 51 ሺህ 700 የአሜሪካ ዶላር በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
ትናንት የካቲት 12 ቀን 2013 ዓ.ም አንድ የህዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ከጅጅጋ ወደ ሱማሌላንድ ሲጓዝ በተደረገ ፍተሻ 51 ሺህ 700 የአሜሪካን ዶላር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር እንዳታወቀው ህገ-ወጥ ገንዘቡ የተያዘው ለቶጎውጫሌ ጉምሩክ መቆጣሪያ ጣቢያ በደረሰ ጥቆማ ነው፡፡
የተያዘው ገንዘብ በወቅታዊ ምንዛሪ 2 ሚሊየን 56 ሺህ 62 ብር ዋጋ አለው ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version