Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን በዓለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነ ብርሃን ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በዓለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነ ብርሃን ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።

በውጭ ግንኙነት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባል በመሆን፤ በጤናው ዘርፍ ከድሆች ጓዳ የዘለቀ የህክምና ድጋፍ በመስጠት ሃገራቸውን በፅናት ያገለገሉት ታላቁ ምሁር እንደነበሩም አቶ ደመቀ መኮንን ገልጸዋል።

ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለሙያ አጋሮቻቸው መፅናናትን ተመኝተዋል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version