Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ ግብረ ኃይሉ በጄኔራል ዮሐንስ እየተመራ የማረጋጋት እና መልሶ የመገንባት ሥራውን ይቀጥላል -ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት  በትግራይ ክልል የተከናወኑ ሥራዎችንና ቀጣይ እርምጃዎችን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ።

ውይይቱ የትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ ግብረ ኃይል እና ጊዜያዊ አስተዳደር በተገኙበት ነው የተካሄደው።

ከዛሬ ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ ግብረ ኃይሉ በጄኔራል ዮሐንስ ገብረ መስቀል ተስፋ ማርያም አመራር በመታገዝ የማረጋጋት እና መልሶ የመገንባት ሥራውን ይቀጥላል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version