አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሚሰሩ እጆች ይበረታታሉ በሚል ሁለተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ሞዴል የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽን እና ባዛር በአዲስ አበባ ከተማ ተከፈተ ።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ከከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ ጋር በመሆን ሀገር አቀፍ ኤግዚቢሽን እና ባዛሩን ከፍተዋል ።
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ በዓላትን ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጅ ኤግዚቢሽን እና ባዛራት አምራቹን እና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነትን በማቃለል ረገድ ሚናው የጎላ መሆኑን ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል ።
መሰል ኤግዚቢሽን እና ባዛሮች ከተለመደው ጊዜያዊ አሰራራቸው ተላቀው በዘላቂነት የገበያ ትስስር ሊፈጠርላቸው እንደሚገባ ተናግረው የከተማ አስተዳደሩ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል ።
በሀገር አቀፍ ኤግዚቢሽን እና ባዛሩ ከአዲስ አበባ ከተማ እና ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ከ280 በላይ ሞዴል የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን ለቀጣይ ሰባት ቀናት የሚያቀርቡ ሲሆን ከ4 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር የገበያ ትስስር እንደሚፈጠርላቸው መገለፁን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬቴሪያት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!