Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠ/ሚ ዐቢይ የሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክን መርቀው ከፈቱ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክን መርቀው ከፈቱ።

የፓርኩ የመጀመርያ ምዕራፍ ግንባታ በ50 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን በውስጡ 5 ሺህ 500 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ስምንት የማምረቻ ህንፃዎችን ይዟል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኩ ለማምረቻ ኢንዱስትሪ አስፈላጊ የሆኑ የመሰረተ ልማቶች እየተሟላለት ነው።

ፓርኩ ሀገሪቱ እየተገለገለችበት ከምትገኘው የጁቡቲ ወደብ እና ሌሎች በአቅራቢያ ለሚገኙ ወደቦች በቅርብ ርቀት መገኘቱ በወጪ ንግድ ዘርፍ ለሚሰማሩ አምራቾች ሳቢ ያደርገዋል፡፡

በአላዛር ታደለ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version