Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአፍሪካ ህብረት በቻድ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር እንዲደረግ ጥሪ አቀረበ

The son of Chad's President Idriss Deby, Mahamat Idriss Deby Itno (also known as Mahamat Kaka) and Chadian army officers gather in the northeastern town of Kidal, Mali, February 7, 2013. REUTERS/Cheick Diouara

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአፍሪካ ህብረት በቻድ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ባሳለፍነው ሚያዚያ ወር የሃገሪቱ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኢድሪስ ዴቢ በውጊያ ወቅት በደረሰባቸው የመቁሰል አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል፡፡
ይህን ተከትሎም ሃገሪቱ በልጃቸው በሚመራው ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡
ህብረቱ ማንኛውንም የሽግግር ማራዘሚያ ጊዜ እንደማይቀበልም አስታውቋል፡፡
የቻድ ወታደራዊ ምክር ቤት በበኩሉ በ18 ወራት ውስጥ ምርጫ ለማካሄድ ቃል ገብቷል ፡፡
ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤቱ ስልጣኑን ከተረከበ ጊዜ ጀምሮ መደበኛ የተቃውሞ ሰልፎች የተካሄዱ ሲሆን በርካታ ማህበረሰብ አንቂዎችም ለእስር ተዳርገዋል ነው የተባለው፡፡
ምንጭ፡-ቢቢሲ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version