Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የጌዴኦ ዞን የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ስብሰባውን አካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጌዴኦ ዞን የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ስብሰባውን አካሄደ፡፡

ስብሰባው በምርጫው አጠቃላይ ሂደትና አጋጥመዋል ባሏቸው ችግሮችና ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነበር፡፡

የምክር ቤቱ አባላት ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በሰላም መርጦ መግባቱ የሚያስደስት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ህዝቡ የሰጠውን ድምፅ ማክበር ደግሞ ከፓርቲዎች እንደሚጠበቅም ነው የተናገሩት፡፡

አያይዘውም የተነሱ ችግሮች በምርጫ ቦርድ ታይተው ምላሽ እስከሚሰጥ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ይገባል ብለዋል፡፡

በታሪክነሽ ሴታ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version