Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አየር መንገዱ ከሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር በጭነት አገልግሎት ያለውን ውል አራዘመ

Liege Airport, August 2009 Refueling. Tank truck. © Pierre Havrenne / Pachacamac

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 8 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቤልጂየሙ ሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር በጭነት አገልግሎት ያለውን ውል ለተጨማሪ አመታት አራዘመ፡፡

አየር መንገዱ ከአውሮፕላን ማረፊያው ጋር ለቀጣዮቹ አምስት አመታት ነው ውሉን ያራዘመው፡፡

በዚህም የሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ እና አውሮፓ መካከል የጭነትና የሎጂስቲክስ አገልግሎት መተላለፊያ ሆኖ እንደሚያገለግል የኤር ካርጎ መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 15 አመታት ከሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር በመተባበር በአውሮፓ የተሳካ የጭነት አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version