Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ትሥሥር ኘሮጀክት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 12፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ሽግግር እና ቀጠናዊ ትሥሥር ኘሮጀክት የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

ከዓለም ባንከ በተገኘ 293 ሚሊየን ዶላር የሚተገበረው ፕሮጀክት ኢትዮጵያ፣ ኬኒያ እና ታንዛንያን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።

ኘሮጀክቱ በየሀገራቱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና ዘርፍ የሚተገበር ነው መባሉን ኢቢሲ ዘግቧል።

በኢትዮጵያ 7 የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና ማዕከላትን ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ መቀመጡ ይታወሳል።

 

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version