Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

12ኛው ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 23፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 12ኛው ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው፡፡
አውደ ርዕዩ እንደ አውሮፓውኑ አቆጣጠር ከመጪው ህዳር 3- 6 ባሉት ቀናት ነው በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄደው፡፡
በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የቆዳና የቆዳ ውጤቶች ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ በተባበሩት መንግስታት የልማት ግብ እና በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
በአውደ ርዕዩ የምስራቅ አፍሪካ የቆዳ አምራቾች ለአለም አቀፉ ፋሽን ብራንድ እና ገዢዎች የተመረጡ ስራዎቻቸውን እና ምርቶቻቸውን እንደሚያቀርቡ ከንግድ እና ኢንደስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version