Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሀረር የኦሮሞ አርቲስቶች ማህበር ተመሠረተ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀረር የኦሮሞ አርቲስቶች ማህበር መመስረቱ ተገለፀ፡፡
ማህበሩ በወጣት እና አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎች አማካኝነት መመስረቱም ነው የተገለጸው።
በምስረታ መድረኩ ላይ የሀረሪ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሚልኬሳ አህመድን ጨምሮ በኦሮሞ ሙዚቃ አንጋፋ የሆኑት አርቲስት መሀመድ ጠዊል ኤሌሞ አሊ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
በርካቶች ህይወታቸውን ከፍለው ዛሬ ያደረሱትን የኦሮሞ ባህልና ኪነ ጥበብ÷ የዛሬው ትውልድ ተቀብሎ ወደ ፊት ለማስቀጠል የማህበሩ መመስረት የኦሮሞ ህዝብን የሚያኮራ መሆኑን ነው የማህበሩ መስራቾች የተናገሩት፡፡
በቲያ ኑሬ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version