Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን ፈተናዎች በድል ተወጥታ የብልጽግና ጉዞዋን ታረጋግጣለች-አቶ ሙሳ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን ችግሮችና ጦርነት በድል ተወጥታ የብልጽግና ጉዞዋን ታረጋግጣለች ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ሙሳ አደም ተናገሩ።
የፓርቲው ጽህፈት ቤት የአመራር አባላትና ሠራተኞች በቢሾፍቱ ከተማ የችግኝ ተከላ በማካሄድ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
ስራ አስፈጻሚው አቶ ሙሳ አደም ኢትዮጵያዊያን አሸባሪውን የህወሓት ቡድንና ድህነትን ድል ማድረግ ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል።
ምንም እንኳን አገሪቷ በጦርነትና በፈተናዎች ውስጥ ብትሆንም ሁሉንም በድል ተወጥታ የብልጽግና ጉዞዋን ታረጋግጣለች ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version