Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሰሜን ኮሪያ አዲስ የረጅም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች

The Academy of National Defense Science conducts long-range cruise missile tests in North Korea, as pictured in this combination of undated photos supplied by North Korea's Korean Central News Agency (KCNA) on September 13, 2021. KCNA via REUTERS ATTENTION EDITORS - THIS IMAGE WAS PROVIDED BY A THIRD PARTY. REUTERS IS UNABLE TO INDEPENDENTLY VERIFY THIS IMAGE. NO THIRD PARTY SALES. SOUTH KOREA OUT. NO COMMERCIAL OR EDITORIAL SALES IN SOUTH KOREA.

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰሜን ኮሪያ አዲስ የረጅም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳኤል ሙከራ ማድረጓ ተሰምቷል፡፡

ሙከራ የተካሄደባቸው አዲሶቹ ሚሳኤሎች 1 ሺህ 500 ኪሎ ሜትር ርቀት መምዘግዘግ መቻላቸው ነው የተገለጸው፡፡

በዚህም አብዛኛውን የጃፓን መልክዓምድር ማዳረስ እንደሚቻል ኮሪያን ሴትንራል የተሰኘው የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል፡፡

የሚሳኤል ሙከራው በሀገሪቱ ላይ የሚቃጣን ማንኛውንም ትንኮሳ ለመመከት እና የጠላት ኃይሎችን ወታደራዊ እንቅስቃሴ መቆጣጠር የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ሙከራው ሀገሪቱ በተጣለባት የኢኮኖሚ ማዕቀብ ሳቢያ አሁን ካለችበት የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ ሆናም አውዳሚ የጦር መሳሪያዎችን የማምረት አቅም እንዳላት ያመላከተ ነው ተብሏል።

በሌላ በኩል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ሰሜን ኮሪያ የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራዎችን ከማድረግ እንድትቆጠብ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቁ ይታወሳል፡፡

ይሁን እንጂ ፒዮንግያንግ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤትን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት የምታደርገውን የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራ ለማስቆም በሀገሪቱ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦችን መጣል እንደሚያስፈልግ ተንታኞች እየተናገሩ ነው፡፡

ምንጭ÷ ቢቢሲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version