Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በምክትል አፈ ጉባኤ ሽታዬ ምናለ የሚመራ ልኡክ ኮምቦልቻ ገባ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል አፈ ጉባኤ ሽታዬ ምናለ የተመራ የሴት ሚኒስትሮችን ያካተተ ልዑክ ኮምቦልቻ ገብቷል፡፡
ምክትል አፈ ጉባኤ ሽታዬ ምናለ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ካሳው ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ ሌሎችም የፌደራል ከፍተኛ ባለስልጣናትና ሚኒስትሮች ናቸው ኮምቦልቻ የገቡት።
የልኡክ ቡድኑ ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጎለታል።
ምክትል አፈጉባኤዋና ሚኒስተሮቹ በደሴ የሚገኙ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዬችን እንደሚጎበኙ እና ውይይት እንደሚደርጉ ይጠበቃል፡፡
በሀብታሙ ተ/ስላሴ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version