Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ዶ/ር ሂሩት ካሳው ወሎ ግንባር በመገኘት የትህነግ ሃይልን እየታገሉ ያሉ የመከላከያ ሰራዊትን አበረታቱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በወሎ ግንባር ፍላቄት ከተማ በመገኘት ለሀገር ህልውና መስዋዕትነት እየከፈሉ የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊትን አበረታተዋል፡፡
እንዲሁም በግንባሩ ከሚገኙ ጀኔራሎች ጋር በቀጣይ ከአመራሩ የሚጠበቀውን ሚና እና ድጋፍ ፤ በህልውና ዘመቻው ሂደት ከህብረተሰቡና ከአመራሩ በሚጠበቀው ድርሻ ዙሪያ ተወያይተዋል።
ጀኔራሎቹም የህብረተሰቡና የወጣቶች ደጀንነት በስንቅ ዝግጅት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ታሪክ የሚዘክረው መሆኑን ገልፀው ÷በዚህም መደሰታቸውን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ዶክተር ሂሩት ካሳው ለሴት መከላከያ ሰራዊት የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ፣በፍላቄት ከተማ ለሚገኙ እናቶችና ህፃናት የሚውል ሃይልሰጭ ብስኩትና ማካሮኒ ድጋፍ አድርገዋል።
ድጋፉንም መቄት ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ መረከባቸውን ከደቡብ ጎንደር ዞን ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version