Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በመዲናዋ የተበላሹ የአስፋልት መንገዶች ጥገና እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በከባድ ዝናብ እና ረጅም ጊዜ በማገልገላቸው ለብልሽት የተዳረጉ የአስፓልት መንገዶችን የጥገና ስራ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡
በዚህም ከዚህ በፊት ለፍሳሽ ማስወገጃ መስመር ለመዘርጋት ሲባል ተቆፋፍሮ ለትራፊክ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ ሆኖ የቆየውን ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ቤተ መንግስት በሚወስደው 450 ሜትር የሚሆን የአስፋልት መንገድ በተያዘው ሳምንት መጀመሪያ ላይ መደበኛ የጥገና ስራ አከናውኖ ለትራፊክ ክፍት ማድረጉንም ገልጿል፡፡
በተጨማሪም ባለስልጣኑ÷ በአገልግሎት ብዛት ለብልሽት ተዳርገው የነበሩትን ከፍል ውሀ ዘውዲቱ ሆስፒታል እና ከሜክሲኮ አደባባይ አፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት ድረስ የቀኝ መስመር የአስፋልት መንገዶች ጥገና አከናውኛለሁ ነው ያለው፡፡
በተያዘው በጀት ዓመትም ከ568 ኪ.ሜ በላይ ልዩ ልዩ የመንገድና የድሬኔጅ መስመሮችን ለመጠገን እቅድ መያዙን ከአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version