Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የደቡብ ክልል ምክር ቤት ለ3 የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት ሹመት ሰጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ምክር ቤት ለ3 የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት ሹመት ሰጥቷል፡፡
ከኢዜማ፣ ከኢሶዴፓ እና ከጌህዴን የፖለቲካ ፓርቲዎች ለተውጣጡ ሦስት ሰዎች ነው ሹመቱ የተሰጣቸው፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
1. አቶ ኦንጋዮ ኦዳ፥ ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)፥ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ፣
2. አቶ ሎምባ ደምሴ ፥ ከኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ(ኢሶዴፓ)፥ የመንግስት የልማት ድርጅት ተቆጣጣሪ ሃላፊ እና
3. አቶ ተመስገን ፈይሳ፥ ከጌዲኦ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ጌህዴን) የክልሉ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር
ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version