Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አልማ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበበ፣ ጥቅምት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አልማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡
አሸባሪው ህወሓት ባደረገው ወረራ የአማራ እና የአፋር ክልል ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በልዩ ልዩ መጠለያ ጣቢያዎች ለመኖር መገደዳቸው ይታወቃል፡፡
ወይዘሮ ንጋቷ ዘውዴና አቶ ስሜነህ አበሻ÷ በርካታ ድጋፎችን ሲያደረጉ መቆየታቸውን ጠቁመው÷ ድጋፉም ወደ ቀያቸው ተመልሰው እስኪቋቋሙ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል፡፡
ተፈናቃዮቹም በበኩላቸው ለሚደረግላቸው ድጋፍ አመስግነው÷ በድጋፍ ስርጭቱ በኩል የሚታዩ ውጣ ውረዶች እንዲስተካከሉ ጠይቀዋል፡፡
በዚህም ለሕጻናት፣ ለሚያጠቡ እናቶች እና ለነፍሰ ጡሮች የተለየ እንክብካቤ እና ድጋፍ ቢደረግላቸው÷ መንግሥት ጦርነቱን በአጭር ጊዜ ቋጭቶ ወደ ቀያቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ በፍጥነት ቢመቻች የሚል አስተያየትና ጥቆማ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም በክፉ ቀን የሚደርስ ወገን ስላላቸው መኩራታቸውን ገልፀዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version