Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ለኢትዮጵያ ህልውና ሕይወታችንን ለመክፈል ዝግጁነን አሉ ወጣቶች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገር የማዳን ጉዳይ የተወሰነ አካል ባለመሆኑ ሁሉም ዜጋ ሀገርን ማዳንና አሸባሪው ህውሃት ለማጥፋት መነሳት አለበት ሲሉ የሀረሪ ክልል ወጣቶች ገልጸዋል፡፡
ሀገር ከሁሉም ይቀድማል በመሆኑም ሁሉም ዜጋ በተለይም ወጣቱ ሀገሩን ለማዳን መዘጋጀትና የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበትም ነው ወጣቶቹ ያሳሰቡት፡፡
አሸባሪው ህውሓት የመላው ኢትዮጵያውያን ጠላት ነው፤ በመሆኑም ሁሉም ዜጋ የሀገሪቱን ጠላት ለመመከት መዘጋጀት ይገባልም ማለታቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከዚህ ቀደም ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ደም በመለገስና የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ድጋፍ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ወጣቶቹ÷ አሁንም ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተነሳውን ቡድን ለመደምሰስ እስከ ግንባር ለመዝመትና ሀገራቸውን ለመታደግ ዝግጁ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version