Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ ÷ ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ ነው ብለዋል፡፡

ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡:

አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን÷ በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡

በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች መገኘታቸውን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Exit mobile version