Fana: At a Speed of Life!

የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ ÷ ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ ነው ብለዋል፡፡

ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡:

አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን÷ በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡

በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች መገኘታቸውን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.