Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 11 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ጎን ለጎን ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር መወያየታቸውን ገለጹ፡፡

በዚህም ከፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ፣ ከፕሬዚዳንት ፌሊክስ ቲሼኬዲ፣ ከፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ እና ከፕሬዚዳንት ኢቫሪስቴ ንዳዪሺሚዬ ጋር ተገናኝተው መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

ከሀገራቱ መሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይትም በቀጣናዊ እና በጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ነው ያመላከቱት፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version